ለመጋቢዎች እና ለቤተክርስቲያን መሪዎች የተዘጋጀ የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ደረጃ።
ያልሰለጠኑ እና በቂ ስልጠና የሌላቸውን መጋቢዎች እና የአገልግሎት መሪዎች ችግርን ለመፍታት ይቀላቀሉን።
ተልዕኮ
ሪ-ፎርማ (Re-Forma) በዓለም ዙሪያ ያሉ መደበኛ ያልሆኑ (informal and non-formal) የሥልጠና ፕሮግራሞችን ለማገልገል የቆመ ሲሆን ዓላማውም፦
- ለጥራት ማረጋገጫ የአሠራር ሥርዓትን ማዘጋጀት፤
- በርካታ የአገልግሎት ስልጠና ፕሮግራሞችን አንድ ለማድረግ፣ ለማቅለል እና ለማሟላት መርዳት፤
- በውጤት እና በተፅዕኖ ላይ የተመሠረተ የምዘና መድረክ ማቅረብ፤
- አዳዲስ ፕሮግራሞችን ማበረታታት እና መደገፍ ነው።
እድገታችን
ሀገሮች ቡድኖቻቸውን አስመዝግበዋል
ለአስተባባሪዎች የሚሆኑ QATIs በ15 ሀገሮች ተካሂደዋል
የስልጠና ቡድኖች በመላው ዓለም ተመዝግበዋል
የሪ-ፎርማ አስተባባሪዎች በመላው ዓለም ሰልጥነዋል
የተለያዩ ቋንቋዎችን በመጠቀም ለአስተባባሪዎች ማስተማሪያዎች ተዘጋጅተዋል
እስከ ዛሬ የተሰጡ ምስክር ወረቀቶች
ዛሬ ዓለም አቀፏ የወንጌላውያን ቤተክርስቲያን እየገጠማት ያለው ትልቁ ቀውስ አብዛኞቹ መጋቢዎች፣ ሚስዮናውያን እና ክርስቲያን መሪዎች በቂ ስልጠና ያልወሰዱ ወይም ምንም ያልሰለጠኑ መሆናቸው ነው።
ሪ-ፎርማ (Re-Forma) የተቋቋመው ብቃት ላይ በተመሠረቱ ውጤቶች ለተቀረጹ መደበኛ ላልሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ አገልግሎቶች ደረጃዎችን ለማውጣት ነው፤ ይህም በዓለም ወንጌላውያን ኅብረት (World Evangelical Alliance) እውቅና የተሰጣቸውን ዓለም አቀፍ የምስክር ወረቀቶችን ለማግኘት ያስችላል።
የተጽዕኖ ታሪኮች
ሪ-ፎርማ በዓለም ዙሪያ ሕይወትን እና አገልግሎትን እንዴት እየለወጠ እንደሆነ ይመልከቱ። ለዘላቂ ተፅዕኖ ራሳቸውን እና ማኅበረሰባቸውን በማስታጠቅ ላይ ካሉ የቤተክርስቲያን መሪዎች አነቃቂ ምስክርነቶችን ያዳምጡ።
ተጽዕኖአችንቡድንዎን ያስመዝግቡ
በብቃት ለመምራት የሚያስፈልጉ መጠቀሚያዎችን ለራስዎ ወይም ለአገልግሎት ቡድንዎ ያሟሉ።
ሌሎችን እያሰለጠኑም ይሁን የራስዎን ችሎታ እያሳደጉ፣ የምዝገባ ሂደታችን በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባለው የመጽሐፍ ቅዱስ አገልግሎት ስልጠና መንገድን ለመጀመር ቀላል ያደርገዋል።
ቡድንዎን ያስመዝግቡ
የበይነ መረብ (Online) መርሐ ግብር
ለመጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት እና ለውጤታማ አገልግሎት በቆረጡ የክርስቲያን መሪዎች ዓለም አቀፍ ንቅናቄ ውስጥ ይሳተፉ
ለራሳቸው ማጥናት ለሚመርጡ የተዘጋጀው የኦንላይን ፕሮግራማችን፣ በመጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት እና ውጤታማ አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ የክርስቲያን መሪዎች ዓለም አቀፍ ንቅናቄ አካል ሲሆን ይህ ፕሮግራም በዓለም ወንጌላውያን ኅብረት (World Evangelical Alliance) ዋስትና የተሰጠውን እና ለመጀመሪያ ጊዜ መደበኛ ላልሆነ (non-formal) የአገልግሎት ስልጠና የወጣውን ዓለም አቀፍ ደረጃ "የመጽሐፍ ቅዱስ አገልግሎት ስልጠና የምስክር ወረቀት" (Certificate of Biblical Training for Ministry) ያስገኛል።
ይህ ፕሮግራም የሚመራው በቤሪያን ኢንስቲትዩት (Berean Institute) መሆኑን ልብ ይበሉ
አሁን ይመዝገቡየሪ-ፎርማ ውጤቶች
ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ የተቀረጹት ውጤቶቻችን እያንዳንዱ መጋቢ ወይም የአገልግሎት መሪ ሊኖረው የሚገባውን መሠረታዊ እውቀት፣ ክህሎት እና ማንነት (ባሕርይ) ይገልጻሉ።
ነባር የሥርዓተ-ትምህርት ፕሮግራምን ለማሟላትም ይሁን አገልግሎቱን ገና ከጅምሩ ለመጀመር፣ እነዚህ ውጤቶች ተማሪዎች የመጽሐፍ ቅዱስ አገልግሎትን ለመፈጸም የሚያስችል የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ እንደ መመሪያ ያገለግላሉ
ውጤቶቹን ይመልከቱምስክርነቶች
ሪ-ፎርማ በአሁኑ ጊዜ መደበኛ ባልሆነ የስነ-መለኮት ትምህርት ውስጥ ያለውን ተዓማኒነት የመመዘን ትልቅ ክፍተት ይሞላል። በመሪነት ልማት ላይ ለምንሰማራ ሁሉ ልንደርስባቸው የሚገቡ ወሳኝ መለኪያዎችን (ደረጃዎችን) አዘጋጅቷል። 'ኤዥያን አክሰስ' (Asian Access) ሪ-ፎርማ በሚያደርገው ነገር ላይ ጽኑ እምነት አለው፣ ደረጃዎቹንም በሙሉ ልብ ይደግፋል። እነዚህ ሁሉም የስነ-መለኮት ስልጠና ድርጅቶች ሊቀበሏቸው የሚገቡ ደረጃዎች ናቸው —
Rev. Joseph W. Handley,
Jr., Ph.D., President, A3 (formerly Asian Access)
ስለ ተልዕኮ አመራር እና የበለጠ ውጤታማ ደቀ መዝሙር አድራጊዎች ስለመሆን ለተሰጡት ትምህርቶች የሪ-ፎርማ ቡድንን አመሰግናለሁ።
- ትምህርቶቹ ተግዳሮቶችን እንዳሸንፍ እና እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕይወት እንድኖር ረድተውኛል።
- አሁን ሰዎችን ከእግዚአብሔር ፍቅር ጋር በማገናኘት በተልዕኮው ውስጥ እንዲሳተፉ ማነቃቃት እችላለሁ።
- የተቀመጠው አርአያነት አገልግሎት እንድሠራ እና ደቀ መዛሙርት እንዳፈራ ኃይል ይሰጠኛል።
- ለፋይናንስ ሂደቱ ላላችሁ ቁርጠኝነት አመሰግናለሁ፤ ስኬት ሁሉ በእግዚአብሔር ኃይል ነው።
እንደ ኢየሱስ በቀላል አኗኗር መኖርን ተምሬአለሁ፤ ይህም ስለ ዓለማዊ ሀብት ከነበረኝ ጭንቀት ነፃ አድርጎኛል፣ እንዲሁም ለሚያስፈልገኝ ነገር ሁሉ እግዚአብሔርን በማመን ከጭንቀት ነፃ የሆነ ሕይወት ሰጥቶኛል።
ስልጠናው በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ እንኳን ሰላም እንዲኖረኝ፣ እግዚአብሔርን እንዳመሰግን (1 ተሰሎንቄ 5:18) እና ዘወትር የምጸልይ እንድሆን አስተምሮኛል።
አሁን የምሰብከውን በተግባር በመኖር በአርአያነት ለመምራት እና ከአገልግሎት ብዛት አስፈላጊውን እረፍት ለመውሰድ ቃል እገባለሁ።
"ትልቁ ተግባራዊ ጥቅም የምስክር ወረቀቱ ነው፤ ይህም በገጠር አካባቢዎች ያለምንም የህግ እንቅፋት ወንጌልን መስበኬን ለመቀጠል የሚያስፈልገኝን በራስ መተማመን እና አስፈላጊ ሰነድ ይሰጠኛል"
ከእኛ ጋር ይሁኑ
ድጋፍዎ ሌሎቹ ሁኔታ ምንም ሥነ መለኮት ሚኒስቴሪ ስልጠና ለማግኘት የማይችሉ ሺዎች ፓስተሮችና ክርስቲያን መሪዎቹን ለማዘጋጀት ይረዳናል።
ዛሬ ከእኛ ጋር ይሁኑ እና የዓለም ቤተ ክርስቲያን ወደፊት ቅርጽ ለመስጠት ወሳኝ ሚና ይጫወቱ።
ይሳተፉ